Welcome to Lideta Subcity Woreda 8 Administration!       እንኳን ወደ ልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር በሰላም መጡ!       Baga Gara Kutaa Magaalaa Lideta Aanaa 8 Nagaan Dhuftan!

ቁጥራዊ መረጃ

16,000

በወረዳዉ የሚኖር የህዝብ ብዛት

841,211

የወረዳዉ ስፋት m2

2441

የወረዳዉ ከፍታ ከባህር ጠለል በላይ

የዋና ስራ አስፈፃሚዉ መልእክት

የልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር የአገልግለት ዕለትን ለተገልጋይ ብቻ በማዋል የህዝብ እሮሮን ለመቀነስ ብሎም በተገልጋዮች የሚነሱ አንገብጋቢ የሆኑ ጥያቄዎችን በአግባቡ አድምጦ ለመመለስ በሁሉም ጽህፈት ቤቶች አገልግሎትን በአንድ ማዕከል መስጠት ከጀመረ ጊዜያትን አስቆጥሯል ፡፡

በተለይም በተለያዩ ምክንያቶች ለአሳዛኝ ችግሮች የተጋለጡ የህብረተሰብ ክፍሎችን በርህራሄ እና በአክብሮት እያዳመጠ ህግና መመሪያ በሚፈቅደው መንገድ ለሚነሱት ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠትና በመፍታት፤ችግሮችና ቅሬታዎች ወደተነሱበት ተቋማት በቀጥታ ስልክ በመደወልም ጭምር በግልፅ በማነጋገር እልባት እየሰጠ ይገኛል። ይህ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላልና ተገልጋዮቻችን ወደ እኛ ኑ ጥያቄያችሁን አቅርቡ። በእኛ ደረጃ የምንፈታውን ፈጣን ምላሽ እንሰጣለን ። ከኛ በላይ የሆነውን ለሚመለከተው አካል እናስተላልፋለን። የማንፈታውን ከእናንተ ጋር እንግባባለን። ይህ የ2018 የአገልግሎት አሰጣጥ መርሀችን ነው። .... ተጨማሪ ያንብቡ

አቶ ደረጄ ፈይሳ , የልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ
image description

የወረዳዉ አመራሮች

ዜና | Oduu | News
የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ተጀመረ።

በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና በዛሬው እለት ተጀምሯል። ተማሪዎቻችን በእውቀት የታነፁ፣ በራሳቸው የሚተማመኑ እና የተሻለ ውጤት የሚያስመዘግቡ ዜጎች እንዲሆኑ የሚያስፈልጉ ድጋፎች ሁሉ እንደምደረግ ተገልጿል።

image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ የወረዳ 08 ምክር ቤት 13 ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ጉባኤዉን አካሂዷል ።

የወረዳ 08 ምክር ቤት ክብርት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ኑሪያ ኢብራሂም በንግግግ መክፈቻቸዉ በ2018 በጀት ዓመት በረካታ ድሎችን ያስመዘገበበት ዓመት ነዉ ።በ7ኛዉ ሀገራዊ ምርጫ የምክር ቤቱ አባላት ከጅምሩ እስከ መጨረሻው በንቃት በመሳተፍ እንደ ወረዳና እንደ ክፍለከተማችን ዉጤቱ ያማራ መሆኑን ገልፀዋል። በበጀት ዓመቱ በተደረገዉ ክትትልና ድጋፍ አብዛኛዉ ተቋማት ከፍተኛ ዉጤት ያስመዘገቡበት በጀት ዓመት መሆኑን ገልፀዉ እንደ ምክር ቤት የተሰሩ ስራዎች በዋናነት በከተማ ግብርና ሰራዎች ፣በሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች፣በሰዉ ተኮር ስራዎች የማዕድ ማጋራት እና የቤት እድሳት ፣የልማት ስራዎች ከፍተኛ ስራ በምክር ቤቱ መሰራቱን ክብርት አፈ ጉባኤዎ ገልፀዋል ።። የወረዳ 08 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደረጀ ፈይሳ በበጀት ዓመቱ በ9ወር የተሰሩ ስራዎችን ሪፖርት አቅርበዉ የመልካም አስተዳደርና የአገልግሎት አሰጣጥ፣የልማትና የሰዉ ተኮር ስራዎች፣በሰላምና ፀጥታ ጉዳይ፣የትምህርት ጥራትን ማሳደግ፣የኢኒሸቲቪ ስራዎች፣በስራ ዕድል ፈጠራ፣በህገ- ወጥ ስራዎች ፣የኑሮ ዉድነትን ለማረጋጋት በቅዳሜና እሁድ ገበያ ምርቶች መቅረባቸዉ እና የህዝብ ግንኙነትን ማሳደግ በዋናነት ተጠቃሽ ናቸዉ በዚህም መሰረት በዚህ በጀት ዓመት ዘርፈ ብዙ ስራዎች መሰራታቸዉን በቀረበዉ ሪፖርት ላይ ተገልጿል ። አገልግሎት አሰጣጥን ግልፀና ቀልጣፍ ለማድረግ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ የዲጂታል አገልግሎትን በማዳበር የህዝባችንን የመልካም አስተዳደር ችግር ለመፍታት ምቹ ሁኔታን በመፍጠር የተገልጋይንና የባለሙያ እርካታን በማሳደግ ወረዳችንን ከፍ ማድረግ ያሰፈልጋል ሲሉ ዋና ስራ አስፈፃሚዉ ገልፀዋል። ለ7ኛዉ ሀገራዊ ምርጫ እና ለነበሩት የልማት ስራዎች ላይ የወረዳዉ ነዋሪና የምክር ቤት አባላት ለነበራቸዉ ድጋፍ ምስጋና አቅርበዉ ለተጀመሩ የልማት ስራዎችና የጂ +4 ግንባታን ለማጠናቀቅ ድጋፋችሁ አይለየን ሲሉ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል። በበጀት ዓመቱ በርካት የልማት ስራዎች፣የኢኒሸቲቫ ስራዎች እና የኑሮ ዉድነትን ለማረጋጋት በቅዳሜና እሁድ ገበያ ምርቶች መቅረባቸዉ ለነበሩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እነዚ ተግባራቶች ችግር ፈች ናቸዉ ሲሉ ተሳታፊዎቹ ተናግረዋል ። የምክር ቤት አባላቱ የ2ኛ በደበኛ ጉባኤዉን ቃላ ጉበኤ አፅድቆ ወ/ሮ ዮዲት አርሴሞን የወረዳ 08 ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አድርጎ ሾሟል። በቀረበዉ ሪፖርት ላይ ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የሚመለከታቸዉ የጽ/ቤት ኃላፊዎችና ከመድረኩ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል ።

image
image
image
ዜና | Oduu | News
ልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በህዝብ ተሳትፎ የተሰሩ የልማት ስራዎች ለአገልግሎት ክፍት አደረገ።

የወጣቶችና የህፃናትን የስፖርት ተሳትፎን ለማሳደግ በማለም ያስገነባውን የእግር ኳስ ሜዳ ፕሌግራውንድ፣ የአስፓልት መንገድ በዛሬው ዕለት ለአገልግሎት ክፍት አድርጓል። ስነ-ስርዓቱ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ የንግድ ቢሮ ሀላፊ፣ የክፍለ ከተማው አስተባባሪ ኮሚቴና አመራሮች፣ የወረዳ ኃላፊዎች፣ ወጣቶች፣ ነዋሪዎች እና የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች በተገኙበት ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል። የክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ እንደገለፁት ሜዳው ፕሌ ግራውድ የወጣቶች ህፃናት ጊዜያቸውን በአዎንታዊ ተግባራት እንዲያሳልፉ እና የስፖርት ችሎታቸውን እንዲያዳብሩ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ብለዋል። የተሰሩ የልማት ስራዎች ለአካባቢው ወጣቶች ነዋሪዎች ጠቃሚ መሆኑን ገልጸው፣ መሰል ልማቶች በቀጣይነት እንደሚስፋፉ ገልፀዋል ። በቀጣይም የህዝቡን ተሳትፎ በማዳበር የማህበረሰብ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ከዚህ በበለጠ በመስራት የወጣቶችን የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት እናረጋግጣለን በማለት ገልፀዋል።

image
image
image
ዜና | Oduu | News
ከተረጂነት በመላቀቅ እራስንና ሀገርን ማበልፀግ እንደሚገባ ተገለፀ ።

በልደታ ክፍለ ከተማ የወረዳ 08 የከተማ ግብርና ጽ/ቤት በኑሮ ዝቅተኛ ላሉ የማህበረሰብ ክፍሎች የእንቁላል ጣይ ዶሮ፣የመኖ እና የኬጅ ስርጭት አደረገ። በዕለቱ ተገኝተዉ የንግግር መክፈቻ ያደረጉት የወረዳ 08 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደረጀ ፈይሳ የሌማት ትሩፋት ተግባርን መንግስት በትኩረት እየሰራበት ያለ ሲሆን ዛሬ የምንሰጣቹሁን መነሻ በማድረግ ከእራስና ከቤተሰቡ አልፎ ለገበያ በማዋል ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጂነት መዉጣት ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ የባለ ብዙ ፀጋዎች ባለሀብት በመሆኗ በሌማት ትሩፋት ተግባራት ላይ ሁሉም ማህበረሰብ በትጋት በመስራት ከተረጂነትና ከልመና በመዉጣት እራሱንና ሀገሩን ማበልፀግ እንዳለበት ተናግረዉ ለቀጣይ ለሚካሄደው 7ኛዉ ሀገራዊ ምርጫ ፍፁም ሰላማዊ እንዲሆን ለወረዳዉ ነዋሪዎች ከወዲሁ ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል። የወረዳ 08 የከተማ ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በላቸዉ አበራ በበኩላቸው ይህ ተግባር በከፍተኛ ደረጃ እየተሰራ ይገኛል ምርትና ምርታማናትን ለማሳደግ በተለያዩ ተግባራት ማህበረሰቡን ተጠቃሚ በማድረግ ያለዉን የኑሮ ዉድነት ለመቀነስ ጽ/ቤቱ በትኩረት መስራቱን ገልፀዋል ። አቶ በላቸዉ አክለዉም የሚሰጧችሁን ዶሮዎች የሚሰጣቹሁን ሙያዊ ክትትልና ድጋፍ በመቀበል የዶሮዎች ጤና በመጠበቅ ከራሳችሁ አልፋቹህ ለገበያ በማዋል ተጠቃሚነታቸዉን ማረጋገጥ እንዳለባቸዉ መልዕክት አስተላልፈዋል ። የካቲት 10/6/2018 ዓ.ም

image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር የተቀናጀ ሞዴል ብሎኮችን በመፍጠር ምቹ፣ ማራኪ እንዲሁም ውብና ጽዱ የመኖሪያ መንደር ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል።

የህብረተሰቡን አኗኗር ዘይቤ እየቀየሩ፤ እያዘመኑ የሚገኙ የተቀናጀ ሞዴል የብሎክ ስራ በልደታ ክ/ከተማ ውስጥ ብሎኮችን የማዘመን ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በክፍለ ከተማ አስተዳደር ህብረተሰቡን በማስተባበር ‎ሞዴል ብሎኮችን በመፍጠር ፅዱ፣ ምቹና ውብ እንዲሁም ማራኪ አካባቢን መፍጠር ያስፈልጋል በማለት አስተዳደርሩ ሰንቆ በተነስው ተግባር በሁሉም ወረዳዎች እና ብሎኮች ተግባሩ ተጠናክሮ ቀጥሏል። "በአዲስ እይታ የልደታ ከፍታ" እቅድ አንዱ ግብ የተቀናጀ ሞዴል ብሎክ መፍጠር ሲሆን ምቹና ውብ እንዲሁም ማራኪ አካባቢ እንዲፈጠር ከነዋሪው ጋር በመቀናጀት እየተሰራ ይገኛል። በተፈጠረው የተቀናጀ ሞዴል ብሎክ የክ/ከተማው ነዋሪዎች አካባቢያቸውን ለኑሮ ምቹና ተስማሚ እንዲሁም ሳቢ እንዲሆኑ ብሎኮቹን በማልማት፣ በማፅዳት፣ በማስዋብ የተለያዩ ተግባራት እያከናወኑ ይገኛል፡፡ አስተዳደሩ ሞዴል ብሎኮችን አጠናክሮ በማስቀጠል ሌሎች ተጨማሪ ምቹ ብሎኮችን በመፍጠር አካባቢያቸውን ምቹ፣ ውብና ጽዱ እና ማራኪ መኖሪያ መንደር ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል። እየተከናወኑ ከሚገኙት የተቀናጀ ሞዴል ብሎክ ተግባራት መካከል በጽዳት፣ በአረንጓዴ ልማት፣ በከተማ ግብርና፣ በሰላምና ፀጥታ፣ ECD፣ በውስጥ ለውስጥ መብራት፣ የመሳሰሉት ስራዎች ተካተውበታል።

image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ምክር ቤት አባላት በወረዳው በኢንሼቲፍ የተሰሩ ስራዎችን የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደረጄ ፈይሳ አስጎብኝተዋል።

አቶ ደረጄ እነዚህ ስራዎች በባለሀብቶች እና በነዋሪዎች በጎ ፈቃደኝነትና ትብብር የተሰሩ ናቸው። የተጠናቀቁት አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል በግንባታ ላይ ያሉት ደግሞ በቅርቡ ተጠናቀው ወደ ስራ ይገባሉ በማለት ተናግረዋል። በጉብኝቱም በጣም መደሰታቸውንና እንደዚህ አይነት ስራዎች አዲስ አበባን ለማስዋብ እየተሰራ ያለውን ስራ በእጅጉ የሚደግፍ ነው ሲሉ የምክር ቤት አባላቱ ተናግረዋል።

image
image
image

አቅጣጫ ጠቋሚ

በወረዳዉ ህንፃ ዉስጥ ያሉ ፅህፈት ቤቶች አቅጣጫ ጠቋሚ

ግራውንድ ፍሎር የሚገኙ ጽ/ቤቶች

ሲቪል ምዝገባና ነዋሪዎች አገልግሎት ጽ/ቤት

አንደኛ ፎቅ የሚገኙ ጽ/ቤቶች

ንግድ ጽ/ቤት

ገቢዎች ጽ/ቤት

ሁለተኛ ፎቅ የሚገኙ ጽ/ቤቶች

ስራና ክህሎት ጽ/ቤት

ሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት

የህፃናት ማቆያ ዴይኬር

ሶስተኛ ፎቅ የሚገኙ ጽ/ቤቶች

ፐብሊክ ሰርቪና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት

ፓርቲ ጽ/ቤት

አራተኛ ፎቅ የሚገኙ ጽ/ቤቶች

ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት

ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ጽ/ቤት

ምክር ቤት

ከተማ ግብርና ጽ/ቤት

ትምህርት ጽ/ቤት

አምስተኛ ፎቅ የሚገኙ ጽ/ቤቶች

ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት

ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት

ህብረት ስራ ጽ/ቤት

ወጣትና ስፓርት ጽ/ቤት

ስድስተኛ ፎቅ የሚገኙ ጽ/ቤቶች

ፋይናንስጽ/ቤት

ፅዳትና ከተማ ውበት ጽ/ቤት

ቤተመጽሀፍት

ሰባተኛ ፎቅ የሚገኙ ጽ/ቤቶች

ዋና ስራ አስፈፃሚ

ዋና ስራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት