ዜና | Oduu | News
በልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር የተቀናጀ ሞዴል ብሎኮችን በመፍጠር ምቹ፣ ማራኪ እንዲሁም ውብና ጽዱ የመኖሪያ መንደር ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል።

የህብረተሰቡን አኗኗር ዘይቤ እየቀየሩ፤ እያዘመኑ የሚገኙ የተቀናጀ ሞዴል የብሎክ ስራ በልደታ ክ/ከተማ ውስጥ ብሎኮችን የማዘመን ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በክፍለ ከተማ አስተዳደር ህብረተሰቡን በማስተባበር ‎ሞዴል ብሎኮችን በመፍጠር ፅዱ፣ ምቹና ውብ እንዲሁም ማራኪ አካባቢን መፍጠር ያስፈልጋል በማለት አስተዳደርሩ ሰንቆ በተነስው ተግባር በሁሉም ወረዳዎች እና ብሎኮች ተግባሩ ተጠናክሮ ቀጥሏል። "በአዲስ እይታ የልደታ ከፍታ" እቅድ አንዱ ግብ የተቀናጀ ሞዴል ብሎክ መፍጠር ሲሆን ምቹና ውብ እንዲሁም ማራኪ አካባቢ እንዲፈጠር ከነዋሪው ጋር በመቀናጀት እየተሰራ ይገኛል። በተፈጠረው የተቀናጀ ሞዴል ብሎክ የክ/ከተማው ነዋሪዎች አካባቢያቸውን ለኑሮ ምቹና ተስማሚ እንዲሁም ሳቢ እንዲሆኑ ብሎኮቹን በማልማት፣ በማፅዳት፣ በማስዋብ የተለያዩ ተግባራት እያከናወኑ ይገኛል፡፡ አስተዳደሩ ሞዴል ብሎኮችን አጠናክሮ በማስቀጠል ሌሎች ተጨማሪ ምቹ ብሎኮችን በመፍጠር አካባቢያቸውን ምቹ፣ ውብና ጽዱ እና ማራኪ መኖሪያ መንደር ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል። እየተከናወኑ ከሚገኙት የተቀናጀ ሞዴል ብሎክ ተግባራት መካከል በጽዳት፣ በአረንጓዴ ልማት፣ በከተማ ግብርና፣ በሰላምና ፀጥታ፣ ECD፣ በውስጥ ለውስጥ መብራት፣ የመሳሰሉት ስራዎች ተካተውበታል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ምክር ቤት አባላት በወረዳው በኢንሼቲፍ የተሰሩ ስራዎችን የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደረጄ ፈይሳ አስጎብኝተዋል።

አቶ ደረጄ እነዚህ ስራዎች በባለሀብቶች እና በነዋሪዎች በጎ ፈቃደኝነትና ትብብር የተሰሩ ናቸው። የተጠናቀቁት አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል በግንባታ ላይ ያሉት ደግሞ በቅርቡ ተጠናቀው ወደ ስራ ይገባሉ በማለት ተናግረዋል። በጉብኝቱም በጣም መደሰታቸውንና እንደዚህ አይነት ስራዎች አዲስ አበባን ለማስዋብ እየተሰራ ያለውን ስራ በእጅጉ የሚደግፍ ነው ሲሉ የምክር ቤት አባላቱ ተናግረዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
''በመደመር መንግስት እይታ፣ የዘርፎች እመርታ!!'' በሚል መሪ ቃል የጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ አቅጣጫዎች ያለበት ደረጃ የወረዳው ጠቅላላ አመራሮች በተገኙበት በስፋት ተገመገመ።

የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 አስተዳደር ''በመደመር መንግስት እይታ፣ የዘርፎች እመርታ !!'' በሚል መሪ ቃል የጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ አቅጣጫዎች ያለበት ደረጃ የወረዳው ጠቅላላ አመራሮች በተገኙበት በስፋትና በጥልቀት ተገምግሟል። በግምገማ መድረኩ በዋነኝነት:- የሌማት ትሩፋት የንቅናቄ ስራዎችን፣ የስራ ዕድል ፈጠራ ስራዎች፣ ከሰው ተኮር ተግባራት፣ የተቀናጀ ሞዴል ብሎክ ከመፍጠር፣ ከሪፎርም ስራ አኳያ የተሰሩ ተግባራት አፈፃፀም ፣ በሪፓርት በዝርዝር ቀርቦ በስፋት ተገምገሟል። በመጨረሻም የተያዙት ዕቅዶች ልዩ ትኩረት የሚፈልጉ በመሆናቸው በውጤት ለማጠናቀቅ ሁሉም አመራር በቁርጠኝነትና በጊዜ የለኝም መንፈስ ሊረባረብ እንደሚገባ አቅጣጫ ተቀምጧል። ታህሳስ 13/2018 ዓ.ም

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 አስተዳደር ህዝባዊ የዉይይት መድረክ ተካሔደ።

በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 አስተዳደር "የጉባ ብስራቶች፤ የመደመር መንግስት ትሩፋቶች" በሚል መሪ ቃል የሕዝባዊ የውይይት መድረክ በዛሬዉ እለት ተካሔዷል። በወረዳዉ በተካሔደው የውይይት መድረክ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶችና ሴቶች፣ የንግዱ ማህበረሰብ፣ ባለሀብቶችና ምሁራንን ጨምሮ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች ተሳታፊ ሆነዋል። የጉባ ብስራቶች የመደመር መንግስት ቱሩፋት በሚል ርዕስ ከዚህ ቀደም በተለያዩ የሕዝብ መድረኮች ላይ ከነዋሪዎቻችን ለተነሱ ጥያቄዎች፣ ቅሬታዎች እና አስተያየቶች በተግባር የተሰጡ ምላሾች፣ እንዲሁም ቀሪ ሥራዎችን አስመልክቶ በወረዳዉ ዋና ስራ አስፈፃሚ በአቶ ደረጄ ፈይሳ በዝርዝር ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል። በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 በተካሔደው የህዝብ የውይይት መድረክ አቶ ገዛኸኝ ዴሲሳ የአዲስ አበባ ፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ዳይሬክተር ፣ወ/ሮ ተስፋነሽ ጋሻው የክፍለ ከተማው ንግድ ፅ/ቤት ሀላፊና የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደረጄ ፈይሳ በጋራ መርተውታል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በከተማችን በተለያዩ የልማት ሥራዎች አስደናቂ ስኬቶች የተመዘገቡት መንግሥትና ሕዝብ አንድ ሆነው በመቀናጀትና በመናበብ ሊፈጽሟቸው በመቻላቸው መሆኑን በውይይቱ ተብራርቷል። በውይይቱ በመንግሥትና በሕዝብ ትብብር የተሰሩ በርካታ ሥራዎችን እና የተመዘገቡ ውጤቶችን ይበልጥ ለማጠናከር፣ እንዲሁም የሕዝብን ተሳትፎ ይበልጥ በሚያረጋግጡ ቀጣይ የጋራ ዕቅዶች ላይ ዳር ማድረስ እንደሚደሚባ መግባባት ተፈጥሯል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
የመደመር መንግሥት እይታን ፣የዘርፎች እመርታ በማብዛት የኢትዮጵያን ብልጽግና እናረጋግጣለን!!!

‎ ‎በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት "በመደመር መንግሥት እይታ፣ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ቃል የሚሰጠው አራተኛ ዙር የብልጽግና ታችኛው አመራር እና አባላት የአቅም ግንባታ ስልጠና ዛሬ ተጠናክሮ ቀጥላል ። ‎ ‎በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን ስብሃት መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት "በመደመር እይታ የግብርና እና ገጠር ትራንስፎርሜሽን" ፥ "የቱሪዝም" ፥ "የአምራች ኢንዱስትሪ እና ከተማ ልማት እመርታ" በሚሉ አራት ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ የአመራራችንና የአባላችን የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት ለማረጋገጥ ትልቅ ድርሻ እንዳለው ገልፀዋል።አራተኛው ዙር የብልጽግና ታችኛው አመራር እና አባላት የአቅም ግንባታ የስልጠና ሰነድ በማቅረብ የስልጠና ዓላማ አባሉ በየደረጃው የሚገኝ ታችኛው አመራር እና አባላት መንግሥት ለነዚህ ዘርፎች የሰጠውን ትኩረት በመረዳት የብልጽግና እሴት እና የመደመር መንግሥት የአባልነት ባህሪን በመላበስ የተጀመረውን ሀገራዊ የከፍታ ጉዞ በውጤታማነት በመደገፍ የሚያስችል አቅም ነው። በመድረኩ በመደመር መንግሥት እይታ፣ የዘርፎች እመርታ" በሚል መሪ ቃል የሚሰጠው ስልጠናው ዋና አላማ በፓርቲያችን እሳቤዎች ፣ በመንግስት ፖሊሲዎች የጋራ እሳቤ በመያዝ ሁለገብ ግንባር ቀደም የሆኑ አመራር እና አባል ለመፍጠር ለሚደረገው ሁለንተናዊ የብልፅግና ጉዞ ለማረጋገጥ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር እና ቀጣይ በስኬቶቻችን ተሸላሚ ለመሆን የአመራሩንና የአባሉ የአስተሳሰብ አንድነት እንደሚገነባ እና ለበለጠ ተልዕኮ ስኬት እምርታ ማረጋገጥ ተክቶ በመስራት ለቸግባር ስኬታማነት ማረጋገጥ ስልጠናው አይነተኛ ሚና እንዳለው መድረኩን የመሩት የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን ስብሃት ገልፀዋል። ‎ በማጠቃለያም የስልጠና ተሳታፊዎች የስልጠና ዓላማ አባሉ በየደረጃው የሚገኝ ታችኛው አመራር እና አባላት መንግሥት ለነዚህ ዘርፎች የሰጠውን ትኩረት በመረዳት የብልጽግና እሴት እና የመደመር መንግሥት የአባልነት ባህሪን በመላበስ የተጀመረውን ሀገራዊ የከፍታ ጉዞ በውጤታማነት በመደገፍ የሚያስችል አቅም ግንባታ ስልጠና መሆኑን አስፈላጊ እንደሆነም ገልጿል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ የወረዳ 08 አስተዳደር በኢቶ ኮደርስ አርቴፊሻል ኢንተለጀስንስ ትግበራ ዙሪያ ለስራ ሂደቶች ግንዛቤ ሰጠ።

በዕለቱም ተገኝተዉ ንግግር ያደረጉት የወረዳ 08 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደረጀ ፈይስ ዘመኑ የቴክኖሎጂ ስለሆነ በኢቶ ኮደርስ እራሳችሁን በማበልፀግ ስራዎችን በአጭር ጊዜ በመስራት እና ቀልጣፍ አገልግሎትን በመስጠት የማህበረሰቡን እርካታ በማሳደግ ዉጤታማ መሆን ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል ። የልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 08 የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ የሆኑት አቶ ሰለሞን ስበአት እንደገለጹት የኢቶ ኮደርስ ተግባር በአገራችን ለውጥ የሚያመጣ ስለሆነ ሁሉም የወረዳችን ሰራተኞች ቶሎ ወደ ተግባር መግባት አለባቸው ብሏል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በ8 ቀናት ውስጥ የምከናወኑ የፓርቲ እና የመንግስት መደበኛ ስራዎች ዕቅድ የጋራ ተደርጓል።

የልደታ ክፍለ ከተማ የወረዳ 8 አስተዳደር በ8 ቀናት በልዩ የምተገበሩ ተግባራት መደበኛ የመንግስትና የፓርቲ ስራዎችን ዙሪያ ከቀጠና አደረጃጀቶች ጋር ውይይት አድርጓል። መድረኩን የመሩት የወረዳ 8 ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን ስበአት በ8 ቀናት ውስጥ በልዩ ትኩረት በተቋምና በክላስተር የምሰሩ ስራ ዕድል ፈጠራ፣የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ተግባራት፣ጤና መድህን፣የገቢ አሰባሰብ ስራዎች ፣ተረጅነት ቅናሳ እና የፓርቲ አጠቃላይ ስራዎች በቅንጂት መስራት አለብን ብሏል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ የወረዳ 08 ስራና ክህሎት ጽ/ቤት በተለያዩ የንግድ ዘርፍ ለተደራጁ ስራ ፈላጊዎች ለተከታታይ 3 ቀናት የሚቆይ የቴክኒክ ክህሎት ስልጠና ሰጠ።

የወረዳ 08 ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አታላይ ስሜነህ በተለያዩ የንግድ ዘርፎች ተደራጅቶ ለመስራት የሲኦሲ ሰርተፍኬት ስለሚያሰፈልግ ይህን የቴክኒክ ክህሎት ስልጠና ያለምንም መቆራረጥ መዉሰድ አለባችሁ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። የተግባረድ ኮሌጅ የቢዝነስ አሰልጣኝ የሆኑት ወ/ሮ ራሔል ስልጠናዉን በመስጠት ላይ ይገኛሉ ይህም ስልጠና ወደፊት ለሚሰሩት ስራ ውጤታማ እንዲሆኑ እንደሚረዳቸው ገልፀዋል ።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ የወረዳ 08 ስነ-ምግባርና ፀረ -ሙስና ቡድን" ትዉልድን በስነ-ምግባር ተቋምን በአሰራር" በሚል መሪ ቃል ከወጣቶች ጋር የፓናል ዉይይት አካሂዷል ።

በአለም አቀፍ ደረጃ ለ22ኛ በሀገራችን ለ21 ጊዜ የሚከበረዉን የፀረ -ሙስና ቀንን አስመልክቶ ከወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ከወጣቶች ጋር የፓናል ዉይይት ተካሄደ። በትዉልድ ግንባታ ላይ እና በተቋማት አሰራር ላይ በትኩረት በመስራት ሙስናን መከላከልና ጥቆማ በመስጠት ሙስናን ማጋለጥ የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት መሆኑን በዉይይቱ ላይ ተገልጿል ። በተቋማት ዉስጥ ብልሹ አሰራርን በማጋለጥ ፣የአሰራር ግልፀኝነትን በማስፈንና የወጣቶችን ስራ አጥነት በመቀነስ የዜጎችን የጋራ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ቡድን ባለሙያ የሆኑት አቶ ሙሉጌታ ያሳብ ተናግረዋል ። የወረዳ 08 ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ በዕምነት ሙስና ለሀገራችን ነቀርሳ የሆነና በማንኛውም ደረጃ ያለዉን ማህበረሰብ የሚጎዳ በመሆኑ ወጣቶች የሙስናን አስከፊነት በመረዳት ጥቆማ በመስጠት ሙስናን መዋጋት አለባችሁ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል ።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
መደበኛ የ10 ቀን ዕቅድ የመንግስት እና የፓርቲ ስራዎች ያሉበት ደረጃ ተገመገመ!!

በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር በ10 ቀናት ንቅናቄ በወረዳ ደረጃ ታቅደው እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት የክፍለ ከተማ ደጋፊ አመራሮች እና አጠቃላይ አመራሩ በተገኙበት ተገምግሟል። የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደረጄ ፈይሳ እንደተናገሩት በቀጣይ አስር ቀናት ስኬታማ ስራዎች መከናወን እንዳለበት አንስተው የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የምናረጋግጠው ተጨባጭ የስራ እድል በመፍጠር፣የኑሮ ውድነቱን በማቃለል እና የሌማት ቱርፋት ስራዎችን በማስፋፋት በመሆኑ እቅዶቻችን በመከፋፈል በቅንጅት በመስራት የቀጣይ አስር ቀናት እቅድ አፈፃፀም ለመሳካት ሁሉም በየደረጃው ያለው አመራር መረባረብ ይገባዋል ብለዋል፡፡ በመጨረሻም አመራሩ የህብረተሰቡን ጥያቄ በሚመልስ ሁኔታ በልዩ ትኩረት በመንግስት ታቅደው እየተተገበሩ ያሉ ተግባሮችን አስተሳስሮ በመስራት የታቀደውን እቅድ ማሳካት እንደሚገባ ተገልጿል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
መደበኛና ወቅታዊ የመንግስትና የፓርቲ ስራዎች በአጠቃላይ አመራር ተገመገመ።

በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር አጠቃላይ አመራር በተገኘበት መደበኛ እና ወቅታዊ የ10 ቀናት ዕቅድ የንቅናቄ ግባራት፣የስራ እድል ፈጠራ ፣የከተማ ግብርና ተግባር ፀጥታ ያለበት ሁኔታ እና የፓርቲ ተግባራት አፈፃፀም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ መድረኩን የመሩት የወረዳዉ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደረጄ ፈይሳ እንዲፈፀሙ የታቀዱ እያንዳንዳቸው ስራዎቻችንን ተግባራዊ በማድረግና የህዝባችን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ በጀመርነው የብልፅግና ጉዞ ላይ ተደማሪ ስኬቶችን እያስመዘገቡ መሄድ ዋናው ትኩረታችን ነው በማለት ገልጿል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በብልጽግና ፓርቲ አሰራር እና አደረጃጀት መመሪያ ዙርያ ለብልፅግና ፓርቲ አባላት ስልጠና ተሰጥቷል።

በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 አስተዳደር የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በተሻሻለው የብልጽግና ፖርቲ አሰራር እና አደረጃጀት ዙርያ ለብልፅግና ፓርቲ ሴት ክንፍ፣ወጣት ክንፍ እና ለመኖሪያ ለአባላት ስልጠና ተሰጥቷል። ስልጠናው የብልጽግና አሰራርና አደረጃጀት መመሪያ በትክክል መረዳት ለተልዕኮ ስኬታማነት ትልቅ ሚና እንዳለው ገልፀው የብልፅግና ፓርቲ አሰራርና አደረጃጀትና መመሪያ ፣ የፓርቲው ዓላማና መለያ እሴቶችን፣ ፕሮግራሞችና ፣ የብልፅግና አስራሮች ፣ የፓርቲው ማህበራዊ መሰረት፣ የአባላት መብትና ግዴታዎች በመተግባር ጠንካራ ተቋምና አደረጃጀት መፈጠርና የሚያሰርፁ እንደሆነ ገልፅዋል። መመሪያው ጠንካራ አደራጃጀት እና አባላትን ለማፍራትና ለማብቃት በማስፈለጉ መዘጋጀቱ የተገለጸ ሲሆን በአቅም ግንባታ፣ በአደረጃጀትና በተልእኮ አሰራር መመሪያን አውቆ ተፈፃሚ እንዲሆንና ፓርቲው የሚፈልገውን ቁመናና ቁርጠኝነት እንዲወጡ ለማስቻል መሆኑ ተገልጿል::

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በኮሪደር ልማት የተዋበው አዲሱ የልደታ ጎዳናዎችና ፕላዛዎች ገፅታ በከፊል!

በኮሪደር ልማት የተዋበው አዲሱ የልደታ ጎዳናዎችና ፕላዛዎች ገፅታ በከፊል!

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ የወረዳ 08 ፐብሊክ ሰርቪስ የሰዉ ሃብት ልማት ጽ/ቤትና ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት የአገልግሎት ቀንን አስመልክቶ ምልከታ አድርገዋል።

በአስተዳደሩ በሚገኙ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሰጭ ተቋማት እና በጽ/ቤቶች የሚገኙ አመራሩም ሆነ ባለሙያዉ አገልግሎት ፈልጓ የመጣዉን ማህበረሰብ ቅንነት በተሞላበት መንፈስ በማገልገል ላይ መሆናቸዉን በተደረገዉ ምልከታ መታየት ተችሏል ።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ለፖሊሶችና ቅጥር ጥበቃዎች በደንብ 148/2016 በቅጥር ጥበቃ መመሪያ ዙሪያ ስልጠና ሰቷል።

በልደታ ክፍለ ከተማ ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት የስልጠና ባለሙያ የሆኑት አቶ ታዴ ባዬ ስልጠናውን ሰተዋል። የጽ/ቤቱ ኋላፊ አቶ ዩሀንስ ሰለሞን መመሪያና ደንብን መሠረት በማድረግ ስራዎች እንዲሰሩና ውጤታማ እንዲሆኑ ለማስቻል ስልጠናው መዘጋጀቱን ተናግረዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ የወረዳ 08 ሴቶች፣ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ለሴት አመራሮች እና ለቡድን መሪዎች የአመራር ክህሎት ስልጠና ሰጠ።

የአንድን ድርጅት ወይም ተቋም የቆመለትን ዓላማና ራዕይ ወደ ተግባር መለወጥ አሊያም ከግብ ማድረስ እንዲችል ሰዎችንና የአመራር ዘዴዎችን ማቀናጀት ፣የአሰራር ዘዴዎችን መንደፍ፣ሃሳቦችን ማመንጨትና አቅጣጫ ማሳየት ሲችል የስነ-አመራር ተግባር መሆኑ በስልጠናዉ ላይ ተገልጿል ። የጽ/ቤቱ ኃላፊ ወ/ሮ ፀሐይ ወርቁ ሴቶች ለተገልጋዮች በቅንነትና በታማኝነት በማገልገል ለሌሎች አርአያ መሆን እንዳለባቸዉና እና መሪነት ለመሆን ያለንን ብቃትና ችሎታ ለማሳየት መታገል መቻል አለብን ሲሉ ተናግረዋል። የወረዳ 08 ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ አይናለም ብርሃኑ መሪነት አርአያ መሆን ነዉ መሪነት ከቤታች የሚጀምረ በመሆኑ ባለንበት ተቋም ላይ አክብሮት በተሞላበት መንፈስ ተገልጋዮችን በማገልገል የመሪነት ብቃታችንን ማሳየት አለብን ሲሉ ተናግረዋል ።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
"ሀገር በቀል እሴቶች ለዘላቂ ሰላም" – ልደታ ወረዳ 08 እና 06 ከወጣቶች ጋር ተወያየ።

ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 እና 06 ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት፣ ወጣቶችን ያሳተፈ "ሀገር በቀል የሰላምና የመቻቻል ለትውልድ እሴቶች ግንባታ" በሚል መሪ ቃል ዙሪያ ሰፊ የውይይት መድረክ ማካሄዱን አስታውቋል። ውይይቱ የተካሄደው ከወረዳው ከተውጣጡ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ከሚወክሉ ወጣቶች ጋር ሲሆን፣ የሰላም ባህልን በወጣቱ ዘንድ ለመገንባት አላማ ያነገበ ነው። ውይይቱን የመሩት የወረዳው ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሄኖክ አበራ እንደተናገሩት፣ ወጣቶች የሀገር ግንባታ ምሰሶ ከመሆናቸው ባሻገር፣ በማኅበረሰብ ውስጥ ሰላምን እና መቻቻልን በማስፈን ረገድ ወሳኝ ሚና አላቸው። አቶ ሄኖክ አክለውም፣ "ሰላም ከውጭ የሚመጣ ሳይሆን በውስጣችን የምንገነባው እሴት ነው። ይህንን ሀገር በቀል የሰላም እና የመቻቻል እሴት ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ በቅድሚያ እኛ ራሳችን የሰላም አምባሳደር መሆን አለብን። ወረዳው የፀረ-ሰላም ኃይሎችን ተጽዕኖ ለመከላከል የወጣቱን ግንዛቤና ተሳትፎ ለማጠናከር ቁርጠኛ ነው" ብለዋል። የልደታ ወረዳ 08 የሰላምና ጸጥታ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ አፈወርቅ ቦጋለ በበኩላቸው፣ የሰላም ማስፈን ሥራ የፖሊስና የጸጥታ አካላት ብቻ ሳይሆን የመላው ኅብረተሰብ በተለይም የንቁ ወጣቶች የጋራ ኃላፊነት መሆኑን አሳስበዋል። አቶ አፈወርቅ እንዳሉት፣ "መቻቻልና ሰላም ሲኖር፣ የሕግ ማስከበር ሥራው ይቀላል። ፖሊስ ወንጀልን ከመከሰቱ በፊት፣ ወጣቶች አለመግባባቶችን በውይይት እንዲፈቱ የማድረግ የሰላም ባህልን ሲያዳብሩ፣ የኅብረተሰብ ደኅንነት ይረጋገጣል። የፌደራል ፖሊስ ኮሚኒቲ ክፍል ከወጣቶች ጋር ተባብሮ በመሥራት የሰላምን ተቋማዊነት ለማረጋገጥ ዝግጁ ነው" በማለት አፅንዖት ሰጥተዋል። በመድረኩ ላይ ወጣቶቹ ሀሳባቸውን በግልጽ በማንሳት፣ ለዘላቂ ሰላም ግንባታ ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
በልደታ ክፍለ ከተማ የወረዳ 08 ፐብሊክ ሰርቪስ የሰዉ ሃብት ልማት ጽ/ቤት፣ምክር ቤትና ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት የአገልግሎት ቀንን አስመልክቶ ምልከታ አድርገዋል።

በአስተዳደሩ በሚገኙ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሰጭ ተቋማት እና በጽ/ቤቶች የሚገኙ አመራሩም ሆነ ባለሙያዉ አገልግሎት ፈልጎ የመጣዉን ማህበረሰብ ቅንነት በተሞላበት መንፈስ በማገልገል ላይ መሆናቸዉን በተደረገዉ ምልከታ መታየት ተችሏል ።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 የብሎክ ካውንስል ጠቅላላ ጉባኤ ተካሄደ፡፡

በጉባኤው ላይ የብሎክ ካውንስል ተጠሪዎች ሰራተኞችና አመራሮች ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን ጉባኤውን በንግግር የከፈቱት የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደረጄ ፈይሳ እንደተናገሩት አስተዳደሩ የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶችን በስፋት እያከናወነ እንደሚገኝ አውስተው፣ ከአስተዳደሩ ጥረት ጎን ለጎን ሕብረተረሰቡ በአካባቢው በሚከናወኑ የልማት ሥራዎች ቀጥተኛ ተሳታፊ በመሆን እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ ልማትን ከማፋጠን ባሻገር በመንግሥትና በሕብረተሰቡ መካከል ያለውን በጋራ የመሥራት ባሕል እንደሚያጠናክር አመላክተዋል፡፡ የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 አስተዳደር ሕብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዮሐንስ ሰለሞን በበኩላቸው የሕብረተሰቡን የልማት ፍላጎት የማሟላት ሥራ በመንግሥት ብቻ የሚከናወን ሳይሆን በህዝቡ ተሳትፎ ሊታገዝ እንደሚገባው ገልጸው በሕብረተሰብ ተሳትፎ በተከናወኑ የልማት ሥራዎች ላይ የብሎክ ካውንስል አደረጃጀቶች በሀብት ማሰባሰብ፣ በግንባታ ሥራዎች አፈጻጸም፣ በአካባቢ ጽዳት፣ በሰላምና ጸጥታ ስራዎችና በሌሎች ተግባራት ከፍተኛ ተሳትፎ እያደረጉ እንደሚገኙ ገልጸው፣ አሁንም የሕብረተሰብ ተሳትፎ ሥራዎችን በማጠናከር ክፍተቶችን በማስተካከል ሁሉም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡ የጉባኤው ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት በተያዘው በጀት ዓመት በሕብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ዘርፍ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸው፤ በቀጣይም ተሳትፏቸውን በማሳደግ በርካታ የልማት ስራዎችን ከመንግሥት ጋር በቅንጅት በመስራት ኃላፊነታቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 አስተዳደር ስራና ክህሎት ጽ/ቤት በወረዳው ለሚገኙ ለስራ ፈላጊ ወጣቶችና ሴቶች የልል ክህሎት ስልጠና ተሰጠ።

በስልጠናው ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ ኢ/ር ይትባረክ ብርሃነ ሰልጣኞች የስራ ዕድል ተጠቃሚ ለመሆን ወደ ስራ ከመግባታቸው በፊት በስራ ላይ ማድረግ ባለባቸው ጉዳዮች ላይ እና ስራቸውን በእውቀት እንዲሰሩ ማድረግ ውጤታማነታቸው ላይ ያለው አስተዋፆ ከፍተኛ በመሆኑ ስልጠናውን በአግባቡ መከታተል ይገባቸዋል ብለዋል ግንዛቤ ለመፍጠር እንደሚረዳም ገልጸዋል። የወረዳው ም/ስራ አስፈፃሚና የስራ ክህሎት ፅ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ የክቴ የማታው ስልጠናው ለስራ ውጤታማነት አቅም የሚፈጥርና የሚያግዝ መሆኑና እንዲሁም በሚመርጡት የስራ ዘርፍ ስራውን በእውቀት እንዲሰሩ ከማገዝ አኳያ ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለውና በቀጣይም ስልጠናውን ወደ ተግባር መቀየር እንዳለባቸው በአፅንኦት ገልፀዋል።

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
የመስቀል ደመራ እና የኢሬቻ በዓል በሰላም እንዲከበር አስተዋጽኦ ላበረከቱ የጸጥታ አካል እና የሰላም ሰራዊት አባላት የምስጋና እና የዕውቅና መርሐ-ግብር ተካሄደ።

በልደታ ክፍለ ከተማ የወረዳ 08 አስተዳደር የመስቀል ደመራና የኢሬቻ በዓል በሰላም እንዲከበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የጸጥታ መዋቅር አባላትና ለሰላም ሰራዊት አባላት የምስጋና ፕሮግራም የተካሄደ ሲሆን በፕሮግራሙ ላይ የወረዳው የጸጥታ መዋቅር አባላትና የሰላም ሰራዊት አባላት ተገኝተዋል። የልደታ ክ/ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍታለሁ ከፍያለሁ በመልዕክታቸው ሰላምን ለማረጋገጥ የከተማ እና የክፍለ ከተማ እና የወረዳ አመራሮች ፣የፌዴራል እና የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት ፣ደንብ ማስከበር፣ የወረዳው የፀጥታና የሰላም ሰራዊቱ አባላት ፣ ወጣቶች ፣ፎሌዎች የማይተካ ሚና በመጫዎት የመስቀል ደመራና ኢሬቻ በዓል በሰላም እንዲከበር ላበረከታችሁት አስተዋጽኦ ከፍተኛ ምስጋና አቀርባለሁ በማለት በቀጣይ ጊዜም ከተለያዩ የጸጥታ ተቋማት ጋር በቅንጅት በመስራት የከተማውን የክፍለ ከተማውን የወረዳውን ሰላምና ጸጥታ ከምን ግዜም በላይ ሳያሳስበን በታላላቅ ሐገራዊ ፕሮጀክቶች በልማቱ ብቻ ምናተኩርበት አመት እና የኢትዮጵያዊን የከፍታን የምናረጋግጥበት እና ቀጣይ ሐገራዊ ምርጫ በአሸናፊነት የምናጠናቀቅበት ይሆናል በማለት ለተሳታፊዎች በፓርቲና እና በራሳቸው ስም አመስግነዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደረጄ ፈይሳ የመሰቀል ደመራና እሬቻ በዓል መጠናቀቅን አስመልክቶ ነዋሪው እና የጸጥታ ተቋማት ጋር በቅንጅት በመስራት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል ከምንጊዜውም በላይ ላደረገው አስተዋፅኦ ምስጋናቸው ላቅ ያለ እንደሆነ ገልፀዋል። በስተመጨረሻም በተለያየ መንገድ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት የሰርተፍኬት እውቅና እና ምስጋና ተካሂዷል እንደዚህ አይነት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ተገልፀዋል። መስከረም 29/2018 ዓ.ም

image
image
image
image
ዜና | Oduu | News
ጠንካራ የፓርቲ ተቋም ለመገንባት የሚያስችል የመልሶ ማደራጀትና የቅድመ ዝግጅት ተግባራት መከናወናቸዉን በሱፐርቪዥን ቡድን ምልከታ ተደርጓል።

በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የተቋቋመ የሱፐርቪዥን ቡድን በልደታ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤትና በወረዳ 1,4 እና 06 ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በመገኘት ሲያካሂድ የቆየውን ሱፐርቪዥን በዛሬው ዕለት በማጠናቀቅ ግብረ መልስ ሰጥቷል። በበጀት አመቱ ጠንካራ የፓርቲ ተቋም ለመገንባት እና የገዥ ትርክት ግንባታን የሚያረጋግጡ የፖለቲካና የአደረጃጀት ዕቅዶች ታቅዶ ወደ ተግባር የተገባ ሲሆን ለዚህ መሳካት የሚያስችሉ የመልሶ ማደራጀት እና የቅድመ ዝግጅት ተግባራት መከናወናቸዉ ይታወቃል። ተግባሩ የተመራበትን አግባብና የተገኙ መልካም ልምዶችን ለማስፋት እና አልቆ ለመፈፀም ክፍተቶችን ለማረም ዓላማ ያደረገ የሱፐርቪዥን ቡድን የፖለቲካና አደረጃጀት ስራዎችን በክፍለ ከተማ፤ በወረዳ፤ በህብረት እና ቤተሰብ ምልከታ አድርጓል። ጠንካራ የፓርቲ ተቋም ለመገንባት የሚያስችል የመልሶ ማደራጀትና የቅድመ ዝግጅት ተግባራት መከናወናቸዉ በግብረ መልስ የተመላከተ ሲሆን በአፈፃፀም ሂደት የተስተዋሉ ክፍተቶችን ፈጥኖ በማረም ጠንካራ የፓርቲ ተቋም ግንባታ ግብ ስኬት ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ ተገልጿል። #prosperiry_lideta_branch. #በአዲስ_እይታ_የልደታ_ከፍታ #ጠንካራ_ፓርቲ_ለጠንካራ_መንግስት

image
image
image
image