image
image
image
image
image

ጠንካራ የፓርቲ ተቋም ለመገንባት የሚያስችል የመልሶ ማደራጀትና የቅድመ ዝግጅት ተግባራት መከናወናቸዉን በሱፐርቪዥን ቡድን ምልከታ ተደርጓል።

ጥቅምት 4, 2017
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የተቋቋመ የሱፐርቪዥን ቡድን በልደታ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤትና በወረዳ 1,4 እና 06 ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በመገኘት ሲያካሂድ የቆየውን ሱፐርቪዥን በዛሬው ዕለት በማጠናቀቅ ግብረ መልስ ሰጥቷል። በበጀት አመቱ ጠንካራ የፓርቲ ተቋም ለመገንባት እና የገዥ ትርክት ግንባታን የሚያረጋግጡ የፖለቲካና የአደረጃጀት ዕቅዶች ታቅዶ ወደ ተግባር የተገባ ሲሆን ለዚህ መሳካት የሚያስችሉ የመልሶ ማደራጀት እና የቅድመ ዝግጅት ተግባራት መከናወናቸዉ ይታወቃል። ተግባሩ የተመራበትን አግባብና የተገኙ መልካም ልምዶችን ለማስፋት እና አልቆ ለመፈፀም ክፍተቶችን ለማረም ዓላማ ያደረገ የሱፐርቪዥን ቡድን የፖለቲካና አደረጃጀት ስራዎችን በክፍለ ከተማ፤ በወረዳ፤ በህብረት እና ቤተሰብ ምልከታ አድርጓል። ጠንካራ የፓርቲ ተቋም ለመገንባት የሚያስችል የመልሶ ማደራጀትና የቅድመ ዝግጅት ተግባራት መከናወናቸዉ በግብረ መልስ የተመላከተ ሲሆን በአፈፃፀም ሂደት የተስተዋሉ ክፍተቶችን ፈጥኖ በማረም ጠንካራ የፓርቲ ተቋም ግንባታ ግብ ስኬት ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ ተገልጿል። #prosperiry_lideta_branch. #በአዲስ_እይታ_የልደታ_ከፍታ #ጠንካራ_ፓርቲ_ለጠንካራ_መንግስት

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች