image
image
image
image
image

የመስቀል ደመራ እና የኢሬቻ በዓል በሰላም እንዲከበር አስተዋጽኦ ላበረከቱ የጸጥታ አካል እና የሰላም ሰራዊት አባላት የምስጋና እና የዕውቅና መርሐ-ግብር ተካሄደ።

መስከረም 29, 2017
በልደታ ክፍለ ከተማ የወረዳ 08 አስተዳደር የመስቀል ደመራና የኢሬቻ በዓል በሰላም እንዲከበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የጸጥታ መዋቅር አባላትና ለሰላም ሰራዊት አባላት የምስጋና ፕሮግራም የተካሄደ ሲሆን በፕሮግራሙ ላይ የወረዳው የጸጥታ መዋቅር አባላትና የሰላም ሰራዊት አባላት ተገኝተዋል። የልደታ ክ/ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍታለሁ ከፍያለሁ በመልዕክታቸው ሰላምን ለማረጋገጥ የከተማ እና የክፍለ ከተማ እና የወረዳ አመራሮች ፣የፌዴራል እና የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት ፣ደንብ ማስከበር፣ የወረዳው የፀጥታና የሰላም ሰራዊቱ አባላት ፣ ወጣቶች ፣ፎሌዎች የማይተካ ሚና በመጫዎት የመስቀል ደመራና ኢሬቻ በዓል በሰላም እንዲከበር ላበረከታችሁት አስተዋጽኦ ከፍተኛ ምስጋና አቀርባለሁ በማለት በቀጣይ ጊዜም ከተለያዩ የጸጥታ ተቋማት ጋር በቅንጅት በመስራት የከተማውን የክፍለ ከተማውን የወረዳውን ሰላምና ጸጥታ ከምን ግዜም በላይ ሳያሳስበን በታላላቅ ሐገራዊ ፕሮጀክቶች በልማቱ ብቻ ምናተኩርበት አመት እና የኢትዮጵያዊን የከፍታን የምናረጋግጥበት እና ቀጣይ ሐገራዊ ምርጫ በአሸናፊነት የምናጠናቀቅበት ይሆናል በማለት ለተሳታፊዎች በፓርቲና እና በራሳቸው ስም አመስግነዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደረጄ ፈይሳ የመሰቀል ደመራና እሬቻ በዓል መጠናቀቅን አስመልክቶ ነዋሪው እና የጸጥታ ተቋማት ጋር በቅንጅት በመስራት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል ከምንጊዜውም በላይ ላደረገው አስተዋፅኦ ምስጋናቸው ላቅ ያለ እንደሆነ ገልፀዋል። በስተመጨረሻም በተለያየ መንገድ አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት የሰርተፍኬት እውቅና እና ምስጋና ተካሂዷል እንደዚህ አይነት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ተገልፀዋል። መስከረም 29/2018 ዓ.ም

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች