image
image
image
image
image

መደበኛ የ10 ቀን ዕቅድ የመንግስት እና የፓርቲ ስራዎች ያሉበት ደረጃ ተገመገመ!!

ጥቅምት 21, 2017
በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር በ10 ቀናት ንቅናቄ በወረዳ ደረጃ ታቅደው እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት የክፍለ ከተማ ደጋፊ አመራሮች እና አጠቃላይ አመራሩ በተገኙበት ተገምግሟል። የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደረጄ ፈይሳ እንደተናገሩት በቀጣይ አስር ቀናት ስኬታማ ስራዎች መከናወን እንዳለበት አንስተው የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የምናረጋግጠው ተጨባጭ የስራ እድል በመፍጠር፣የኑሮ ውድነቱን በማቃለል እና የሌማት ቱርፋት ስራዎችን በማስፋፋት በመሆኑ እቅዶቻችን በመከፋፈል በቅንጅት በመስራት የቀጣይ አስር ቀናት እቅድ አፈፃፀም ለመሳካት ሁሉም በየደረጃው ያለው አመራር መረባረብ ይገባዋል ብለዋል፡፡ በመጨረሻም አመራሩ የህብረተሰቡን ጥያቄ በሚመልስ ሁኔታ በልዩ ትኩረት በመንግስት ታቅደው እየተተገበሩ ያሉ ተግባሮችን አስተሳስሮ በመስራት የታቀደውን እቅድ ማሳካት እንደሚገባ ተገልጿል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች