image
image
image
image
image

በልደታ ክፍለ ከተማ የወረዳ 08 ሴቶች፣ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ለሴት አመራሮች እና ለቡድን መሪዎች የአመራር ክህሎት ስልጠና ሰጠ።

ጥቅምት 27, 2017
የአንድን ድርጅት ወይም ተቋም የቆመለትን ዓላማና ራዕይ ወደ ተግባር መለወጥ አሊያም ከግብ ማድረስ እንዲችል ሰዎችንና የአመራር ዘዴዎችን ማቀናጀት ፣የአሰራር ዘዴዎችን መንደፍ፣ሃሳቦችን ማመንጨትና አቅጣጫ ማሳየት ሲችል የስነ-አመራር ተግባር መሆኑ በስልጠናዉ ላይ ተገልጿል ። የጽ/ቤቱ ኃላፊ ወ/ሮ ፀሐይ ወርቁ ሴቶች ለተገልጋዮች በቅንነትና በታማኝነት በማገልገል ለሌሎች አርአያ መሆን እንዳለባቸዉና እና መሪነት ለመሆን ያለንን ብቃትና ችሎታ ለማሳየት መታገል መቻል አለብን ሲሉ ተናግረዋል። የወረዳ 08 ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ አይናለም ብርሃኑ መሪነት አርአያ መሆን ነዉ መሪነት ከቤታች የሚጀምረ በመሆኑ ባለንበት ተቋም ላይ አክብሮት በተሞላበት መንፈስ ተገልጋዮችን በማገልገል የመሪነት ብቃታችንን ማሳየት አለብን ሲሉ ተናግረዋል ።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች